የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ልማት ማዕከል የስንዴ ምርት መሰብሰብ መጀመሩን ገለፀ፡፡

ሀምሌ 27/2016 ዓ/ም

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ልማት ማዕከል እንደገለጸው በ2016 የምርት ዘመን ሁለት አይነት የስንዴ ምርጥ ዘርና የግብርና ግብዓት በመጠቀም መዝራቱን አስታውሰው የተዘራዉም የስንዴ ዘር ዘመናዊና ምርጥ ዘር መሆኑን ገልጸው አይነታቸውም "ቀቀባ" ና "ኪንግባርድ" የተባሉ መሆናቸውን አስታውሰዋል። የስንዴ ምርቱ የተሰበሰበውም ዘመናዊ የምርት መሰብሰቢያ መሣሪያ በመጠቀም እንደሆነ የማዕከሉ ዳይሬክተር መ/ር ቀመር ይማም ገልፀዋል፡፡ ይህ የማምረቱ ሂደት ወደፍት ተጠናክሮ ከቀጠለ ለዩኒቨርሲቲዉ በገቢ ምንጭነት ከማገልገሉም በላይ ለመማር ማስተማር ፤ለምርምር ; ለቴክኖሎጂ ሽግግርና ለማህብረሰብ አገልግሎት ከፍተኛ ጥቅም ያለዉ መሆኑን በአንክሮ ገልጸዋል፡፡

ማስታወቂያ

ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና  (NGAT) ምዝገባ የሚካሄደው ከሐምሌ 24 - ነሐሴ 05/2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ የመመዝገቢያው ቅጽ ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በሟሟላት በ https://NGAT.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

 

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለመምህራንና ለትምህርት ቤት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናን በሚመለከት የግንዛቤ ማስጨበጫ ኦረንቴሽን ሰጠ።

ሀምሌ 22/2016 ዓ/ም

ወደ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለሙያ ማሻሻያ ትምህርትና ስልጠና የተላኩትን የትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች እንዲሁም የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንን ስልጠና አስመልክተዉ ከማዕከል ከክቡር የትምህርት ሚኒስቴር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና ከኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አቢይ አህመድ ለስልጣኞቹ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ኦረንቴሽን ከተሰጠ በኋላ ዩኒቨርሲቲዉም በበኩሉ ለስልጣኞቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን፣ ሰልጣኞቹም በዩኒቨርሲቲዉ በሚኖራቸዉ የቆይታ ጊዜና የስልጠናዉን ጠቅላላ ሂደት አስመልክቶ በዩኒቨርሲቲዉ ክፍተኛ አመራሮች ተገቢዉ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።በቆይታቸዉም ወቅት ሰልጣኞች የመጡለትን አላማ ለማሳካት ሁሉም ሰልጣኝ በበኩሉ ተገቢዉን ጥረት እንዲያደርግ አስገንዝበዋል።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የ”GAT”ፈተናና ምዝናን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

ሀምሌ 20/2016 ዓ/ም
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት ክዚህ በኋላ ትምህርታቸዉን በ2ኛና 3ኛ ዲግሪ መቀጠል ለሚፈልጉ መምህራን፣ ሌሎች የመንግስት ሰራተኞችና ግልሰቦች ማሟላት ከሚገባቸዉ መስፈርቶች አንዱ የሆነዉ የGAT(Graduation Admission Test) ፈተናና ምዘናን ወስዶ ማለፍ መቻል ነዉ።
በስልጠናዉ ላይ በመገኘት ስልጠናዉን በንግግርና ሃሳብ በመስጠት ያስጀመሩት የዩኒቨርሲቲዉ የአካዳሚክ፣ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ትንሳኤ ታምራት ናቸዉ። በንግግራቸዉ ካነሷቸዉ ሃሳብ አንዱ የጋት ፈተናን ወስዶ ማለፍ ከተቀመጠዉ አቅጣጫ ዋነኛዉ መስፈርት ሲሆን፣ እያንዳንዱ አመልካች ተማሪ ይሄንን ተገንዝቦ ስልጠናዉን በተኩረትና በመረጋጋት መዉሰድ እንዳለበት አስምረዉበት አሳስበዋል።

Pages