በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ዓ.ም የ1ኛ ሩብ ዓመት የሥራ ክንዉን ሪፖርት ቀርቦ ዉይይት ተካሄደ፡፡

ጥቅምት 27/2017 ዓ.ም

ዩኒቨርሲቲዉ በ2017 ዓ.ም በአንደኛ ሩብ ዓመት ለማከናወን ያቀደዉን ዕቅድ ከመተግበር አንጻር የሥራ ክንዉኑ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮችና የየዘርፉ ኃላፊዎች በተገኙበት ተገምግሟል፡፡

ሪፖርቱ የቀረበዉ በዩኒቨርሲቲዉ የዕቅድ በጀትና ክትትል ሥራ አስፈፃሚ በሆኑት በአቶ መሰለ አለማየሁ ሲሆን በበጀት ዓመቱ በ1ኛ ሩብ ዓመት በሦስት ወራት ዉስጥ የመማር ማስተማሩን ሥራ ጨምሮ ሌሎችንም ተግባራት በየግቡና በተቀመጠለት ስትራቴጅክ ዓላማ መሠረት በማቀናጀት በዝርዝር አቅርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

የጥናትና ምርምር ዉጤቶችን በአለም አቀፍ ደረጃ ዕዉቅና ባላቸዉ ጆርናሎች ላይ ያለ ክፍያ መምህራን የሚያሳትሙባቸዉ መንገዶች ይፋ ሆነ።

ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም

በዩኒቨርሲቲዉ ድጋፍ ከሚደረጉላቸው የጥናትና ምርምር ዉጤቶችን በአለም አቀፍ ደረጃ ዕዉቅና ባላቸዉ ጆርናሎች ላይ ከማሳተም ባሻገር መምህራን ምንም ዓይነት ገንዘብ ሳያስፈልጋቸዉ ማሳተም የሚያስችላቸዉ መንገድ የተመቻቸ ሲሆን እሱም “Enhancing BHU Affiliated Research Publication using PRISMA Methodology: A zero Budgeting Approach” በሚል ርዕስ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት በጉዳዩ ላይ ውይይት በማድረግና መምህራን ሊኖራቸው የሚገባውን ግንዛቤ ከፍ ለማድረግ እንዲሁም አቅጣጫ በማስቀመጥ በዚህ ዙር ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቋዋል፡፡

Pages