Bule Hora University Health Institute hosts "Health Night" program

The program was attended by the university's health science students, the vice president of Academic, Research, Technology transfer and Community Service, Dr. Tinsaye Tamrat, and other leaders and instructors of the university. The Director of the Health Institute, Dr. Safayi Elema,  said that the program was designed to prepare the graduating students for the upcoming exit exam and to showcase their skills and knowledge. Dr. Tinsaye Tamrat, also addressed the participants.

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና ተሰጠ፡፡

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ዓመታት በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት HCP (Himalan Cataract Project ) ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመፈራረም ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል፡፡
በመሆኑም በስምምነቱ መሠረት ለ2ኛ ዙር የድርጅቱ ተወካይ አቶ ሀገሩ ከበደ በተገኙበት ከ17/03/2016-21/03/2016 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ነፃ የአይን ሞራ ግርዶሾ ቀዶ ጥገና በሆስፒታሉ እየተሰጠ ይገኛል፡፡ የቀዶ ጥገና ዘመቻ ሥራዉን በሚመለከት ማብራሪያ የሰጡት በሆስፒታሉ የዓይን ህክምና ስፔሻሊስት ዶ/ር አያኖ ባሳዝን ድርጅቱ "Cure blindness" የሚል መሪ ቃል ይዞ የሚሰራ መሆኑን በመግለጽ የዓይን ሞራ ግርዶሽ በአመዛኙ ሰዎች እድሜያቸዉ  ከ55 በላይ ሲሆን የሚከሰት መሆኑን እና በተጨማርም በዓይን ላይ በሚደርስ አደጋ እና በሌሎች የዓይን በሽታዎች እንዲሁም አብሮ በመወለድ የሚመጣ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

Pages