ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን አስመረቀ
Posted by admin on Wednesday, 25 March 2026መጋቢት 13/2018 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
ዩኒቨርሲቲው ከ15ኛ ዙር ተማሪዎች ምርቃት ጎን ለጎን የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት የተቀላጠፈ እንዲሆን በማድረግና የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ በኩል ትልቅ ሚና የሚጫወቱ እንዲሁም የማህብረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጡ ታስበው የተገነቡ ሦስት ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በትምህርት ሚኒስቴር የምርምር እና ማህብረሰብ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚና የዕለቱ የክብር እንግዳ ክቡር ዶ/ር ሠራዊት ሃንዲሶ እና ለሎችም የትምህርት ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎችና የምዕራብ ጉጂ ዞን አስተዳደር አካላት በተገኙበት አስመርቋል።
























































