በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ማህበር ሥራ አስፈፃሚዎች ምርጫ ተካሄደ።
Posted by admin on Saturday, 19 July 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ ግንቦት 9፣ 2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ እና የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማህበር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደበላሽ መንግስቱ በተገኙበት ከእያንዳንዱ ኮሌጅ ከተወከሉ መምህራን ጋር የጋራ ውይይት ተካሂዶ የማህበሩ ሥራ አስፈፃሚዎች ምርጫ ተካሂዳል።
የማህበሩ ከፍተኛ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው የመጡበትን ዓላማ እና ማህበሩ የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ አኳያም ሆነ የመምህራንን ጥቅማጥቅም ከማስጠበቅ አንፃር እያከናወነ ባለው ሥራ ዙሪያ ገለፃ አድርጓል።


















































