በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ``Cure Blindness``ከተባለ መንግስታዊ ካልሆነ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ነፃ የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና በዘመቻ መልክ እየተሰጠ ይገኛል።
Posted by admin on Saturday, 19 July 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 09/2017 ዓ.ም
በሀገራችን በአይን ህክምና ዙሪያ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከሚሠሩት ግብረሰናይ ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነው ``Cure blindness project``ከቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ጋር የመግባቢያ ስምምነት በመፍጠር ለበርካታ ዞሮች ከክፍያ ነፃ የሆነ የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ከመስጠቱም በላይ በርካታ የህክምና መሣሪያዎችን ጭምር ለግሷል።
በመሆኑም በተመሳሳይ መልኩ ከድርጅቱ ጋር በመተባበር ነፃ የአይን ሞራ ግርዶሽ የቀዶ ህክምና አገልግሎት ከሐምሌ 7/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአይን ህክምና አገልግሎት በዘመቻ መልክ በማስተማሪያ ሆስፒታሉ እየተሰጠ ይገኛል።
























































