በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸዉን እየተከታተሉ ለሚገኙ የ2ኛ ዓመትና ከዚያን በላይ ለሆኑ መደበኛ ተማሪዎች የ‹‹e-SHE ( Student Success Suit ) የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ፡፡
Posted by admin on Thursday, 9 October 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ቡሆዩ)
የ2018 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደት ከመጀመሩ በፊት የe-SHE አስፈላጊነትና አጠቃቀምን በሚመለከት በኢ-ሌርንግ ማናጅመንት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለመደበኛ ተማሪዎች ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡
ሥልጠናዉን የሰጡት በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የኢ-ሌርንግ ማናጅመንት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መ/ር ንጉስ ቢተዉ ሲሆኑ ይህ በመማር ማስተማሩ ሂደት ወሳኝ ድርሻ ያለዉ በመሆኑና በቀጣይም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረጃ የበይነ መረብ የትምህርት አሰጣጥ ሂደት ተጠናክሮ የሚቀጥል በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊዉን ትኩረት ሰጥተዉ እንዲከታተሉ በአንክሮ አሳስቧል፡፡























































