በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የምርምር ሥራዎች ዙሪያ የዉስጥ ግምገማ ተካሄደ፡፡
Posted by admin on Thursday, 9 October 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም፣ 2018 (ቡሆዩ)
በዩኒቨርሲቲዉ የምርምር፤ስርፀትና ሥነ ምግባር ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት ከተለያዩ ኮሌጆች የተወጣጡ ምሁራን የምርምር ሥራዎቻቸዉን አቅርበዉ የዉስጥ ግምገማ ተካሂዶባቸዋል፡፡
በዕለቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ምርምር፤ስርፀትና ሥነ ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር አብነት በቀለ ሲሆኑ ለዉስጥ ግምገማ የቀረቡ የምርምር ሥራዎች በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ዳይሬክቶሬቱ ጭብጥ ተኮር የምርምር ሥራዎችን ለማሰራት ያስቀመጠዉን አቅጣጫ ተከትሎ በተለያዩ ኮሌጆች ምሁራን ፕሮፖዛል ቀርበዉ፤ተገምግመዉና ተቀባይነት አገኝተዉ የተሠሩ የምርምር ሥራዎች ስለመሆናቸዉ በመግለጽ በጋራ የዉስጥ ግምገማ መደረጉ የእርስ በርስ ልምድ ልዉዉጥ እንዲደረግ ታሳቢ በማድረግ እንደ ሆነ ገልፀዋል፡፡


















































