በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ “ባህላዊ ህክምና እና ሀገር በቀል የህክምና ልምዶች ከዘመናዊ ጤና አጠባበቅ ሥርዓት አንፃር፡ ከማወቅ እስከ ትብብር” በሚል መሪ ቃል ዎርክሾፕ ተካሄደ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ ህዳር 01/2018 ዓ.ም (ቡሆዩ)

በሀገር በቀል ህክምና ዕዉቀት ዙሪያ በተናጠል የሚሠሩ ሥራዎችን የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በአንድ ላይ በማገናኘት በዘርፉ የተሻለ ሥራ ለመሥራትና የተመራማሪዎችን አቅም ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ ዎርክሾፕ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከጤና ሚኒስቴር፤ከተለያዩ ወረዳዎች የተጋበዙ የባህልና ቱሪዝም የሥራ ኃላፊዎች እና ከተለያዩ አካባቢዎች የተጋበዙ የባህል ህክምና አዋቂዎች በተገኙበት ዎርክሾፕ ተካሂዷል፡፡

የቡሌ ሆራ የኒቨርሲቲና የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ፡፡

አዲስ አበባ፣ ህዳር 04/2018 ዓ.ም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ

በቡሌ ሆራ የኒቨርሲቲ አካዳሚክ፤ምርምር፤ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬ የተመራ ልዑክ በዛሬዉ ዕለት አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንሲቲትዩት ቢሮ በመገኘት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲቲና የኢትዮጵያ ደን እና ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 07/2018 ዓ.ም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ

ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው ያለውን ብዝሃ ሕይወት በአግባቡ በመጠበቅ ከቱርዝም የሚገኘው ገቢ የሀገር ኢኮኖሚን መደገፍ እንዲችል ከደን እና ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ከባልሥጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኩመራ ዋቅጀራ ጋር የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ፣ምርምር፣ቴክኖሎጅ ሽግግርና ማህብረሰብ አግልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬ ተፈራርሟል።

Pages