ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለ15ኛ ጊዜ 1266 ተማሪዎችን በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።
Posted by admin on Wednesday, 25 March 2026መጋቢት 13/2018
ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ኮሌጆች ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተማሪዎች የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የዞንና ከተማ መስተዳድር አመራሮች ፣የዩኒቨርሲቲው ሴኔት አባላት ፣አባ ገዳዎች፣የሐይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች በተገኙበት በመጀመሪያ ድግሪ 992 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ 269 በሦስተኛ ድግሪ ( Ph.D) 5 ተማሪዎችን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመርቋል።
በምረቃ በዓሉ ላይ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ ንግግራቸውን የጀመሩት የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተመስገን ደበሎ ትምህርት የአመለካከት፣የእውቀት እና የክህሎት በመለወጥ ለሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና የሚያዘጋጅ መሣሪያ መሆኑን እና በዚሁ መልኩ የተለወጠ ዜጋ ለቤተሰቡም ሆነ ለሀገር ለውጥ ይተጋል ሲሉ ገልፀዋል።
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን አስመረቀ
Posted by admin on Wednesday, 25 March 2026መጋቢት 13/2018 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
ዩኒቨርሲቲው ከ15ኛ ዙር ተማሪዎች ምርቃት ጎን ለጎን የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት የተቀላጠፈ እንዲሆን በማድረግና የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ በኩል ትልቅ ሚና የሚጫወቱ እንዲሁም የማህብረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጡ ታስበው የተገነቡ ሦስት ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በትምህርት ሚኒስቴር የምርምር እና ማህብረሰብ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚና የዕለቱ የክብር እንግዳ ክቡር ዶ/ር ሠራዊት ሃንዲሶ እና ለሎችም የትምህርት ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎችና የምዕራብ ጉጂ ዞን አስተዳደር አካላት በተገኙበት አስመርቋል።
Leadership Transition Program at Bule Hora University
Posted by admin on Wednesday, 28 January 2026December 22/2025, A program to exchange knowledge and facilitate a leadership transition was organized for the new President, Dr. Tamasgen Dabalo, and the Deputy President for Administrative and Development Affairs, Mr. Tariku Gamade.
The program included members of the board, with the former President, Dr. Birhanu Lama, sharing insights and experiences with the new President to foster a spirit of collaboration.






















































