በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሥረዓተ ትምህርት ክለሳ በኮፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ተካሄደ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 27/2017 ዓ.ም (BHU)
እንደሚታወቀው በመማር ማስተማሩ ሂደት የትምህርት ጥራትና አግባብነት ለማስጠበቅና ብሎም ለማረጋገጥ ከሚተገበሩት ተግባራት አንዱና ዋናኛው ተዘጋጅቶ በሥራ ላይ ያለውን ሥረዓተ ትምህርት በየግዜው እንደ አስፈላጊነቱ በየደረጃው ባሉት የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ የሥረዓተ ትምህርት ክለሳና ፍተሻ ማድረግ ነው።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ “Invigorated Research Agenda and an overview of Research journey`` በሚል ርዕስ ለመምህራን የግንዛበ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

በቡሌ-ሆራ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 26/2017 ዓ.ም (BHU)
በዩኒቨርሲቲዉ ምርምር፤ስርፀትና ሥነ ምግባር ዳይሬክቶሬት አማካኝነት በምርምር ሥራዎች ላይ ያተኮሩ አቅም ግንባታ ሥልጠናዎች እተሰጡ ይገኛሉ፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና እና እንስሳት ሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ MSC (open Thesis Defense) እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 26/2017(BHU)
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና እና እንስሳት ሳይንስ ኮሌጅ የሁለተኛ ድግሪ ተመራቂ ተማሪዎች MSc in Agricultural economics, Msc in Soil Science, MSc in Sustainable Natural Resources Management ዙሪያ የመመረቂያ ጽሑፋቸዉን በዛሬዉ ዕለት ማቅረብ ጀምሯል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ የግብርና እና እንስሳት ሕክምና ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ዮሐንስ ኡርገሳ ፤ገምጋሚ መምህራንና ሌሎች ተጋባዥ መምህራን የተገኙ ሲሆን ዶ/ር ዮሐንስም በግብርናዉ ዘርፍ የተሻሻሉና በምርምር የተደገፉ የሥራዎችን በመሥራት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፏል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የ5ኛ ዓመት የክሊኒካል ፋርማሲ ተማሪዎች የተለያዩ በጎ አድራጎት ሥራዎችን አከናወኑ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 26/2017 ዓ.ም (BHU)
የኢንስቲትዩቱ 5ኛ ዓመት የክሊኒካል ፋርማሲ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲዉ ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ላለፉት ሁለት ወራት ወደ ማህብረሰቡ በመዉረድ የተለያዩ በጎ አድራጎት ሥራዎችን በማከናወን አፈፃፀሙን በዛሬዉ ዕለት የኢንስቲትዩቱ አመራሮች፤መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት ገምግሟል፡፡

Pages