በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በጥናትና ምርምር ዙሪያ ወርክሾፕ ተካሄደ፡፡
Posted by admin on Wednesday, 6 November 2024ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም
“Transformative Research through Gender lens: Implications for Science, Innovation, and Technology`` በሚል ርዕስ በዩኒቨርሲቲዉ ያሉ ሴት መምህራን የጥናትና ምርምራ ተሳትፎ ማሳደግን ዓላማ ያደረገ የጥናትና ምርምር ወርክሾፕ የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
ወርክሾፑ የዩኒቨርሲቲዉ የምርምር፤ሕትመት፤ሥነ-ምግባርና ሥርፀት ሥራ አስፈፃሚ አስተባባሪነት የተዘጋጀ ሲሆን የክፍሉ ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብነት በቀለ ዩኒቨርሲቲዉ ሥራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ያለዉን የጥናትና ምርምር ጉዞ ሂደት ገለፃ በማድረግ የሴት መምህራን የጥናትና ምርምር ተሳትፎም ከነበረበት 2.8% ወደ 5.6% ከፍ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸዉን ገልጾዋል፡፡