የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ልማት ማዕከል ወቅቱን ጠብቆ ስንዴ መዝራት መጀመሩን ገለፀ፡፡

ሚያዚያ 12/2015 ዓ.ም 
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ልማት ማዕከል ወቅቱን ጠብቆ ስንዴ መዝራት መጀመሩን ገለፀ፡፡
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ልማት ማዕከል በ2015 ዓ.ም ምርት ዘመን በሰላሳ ሄክታር የእርሻ መሬት ላይ ምርጥ ዘርና ግብዓት በመጠቀም ስንዴ መዝራት መጀመሩን አሳዉቋል፡፡የግብርና ማዕከል ዳይሬክተር የሆኑት መ/ር ሀሮ አዱላ እንደገለፁት የተዘሩት የስንዴ ዓይነቶች "ቀቀባና ኪንግ በርድ" የሚባሉ መሆናቸዉን በመጠቀስ ይህም በሄክታር ከ33-35 ኩንታል ምርት ሊገኝ እንደምችል ተናግሯል፡፡
መ/ር ሀሮ አያይዘዉም የእርሻ ሥራዉ ለዩኒቨርሲቲዉ በገቢ ምንጭነት ከማገልገሉም በላይ ለመማር ማስተማር ፤ለምርምርና ለማህብረሰብ አገልግሎት ከፍተኛ ጥቅም ያለዉ መሆኑን በመግለጽ በቀጣይም በግብርና ልማት ማዕከል ሥር የተለያዩ የእርሻ ሥራዎችን በስፋት ለማከናወን እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ 
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ