የቡሌ ሆራ የኒቨርሲቲና የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ፡፡

አዲስ አበባ፣ ህዳር 04/2018 ዓ.ም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ

በቡሌ ሆራ የኒቨርሲቲ አካዳሚክ፤ምርምር፤ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬ የተመራ ልዑክ በዛሬዉ ዕለት አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንሲቲትዩት ቢሮ በመገኘት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲቲና የኢትዮጵያ ደን እና ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 07/2018 ዓ.ም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ

ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው ያለውን ብዝሃ ሕይወት በአግባቡ በመጠበቅ ከቱርዝም የሚገኘው ገቢ የሀገር ኢኮኖሚን መደገፍ እንዲችል ከደን እና ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ከባልሥጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኩመራ ዋቅጀራ ጋር የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ፣ምርምር፣ቴክኖሎጅ ሽግግርና ማህብረሰብ አግልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬ ተፈራርሟል።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከፋነ - አጋ ፋዉንዴሽን ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡

ህዳር 20/2018 ዓ.ም፡ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

ይህ ምሥረታ ወይም ፋዉንዴሽኑ ህዳር 23/2016 ዓ/ም በይፋ ስራ የጀመረ ሲሆን ፤ የተቋቋመበት ዋና ዓላማ ቀደም ሲል 72ኛ የጉጂ አባ ጋዳ በነበሩና የክብር ዶኮቶሬት ተሸላሚ በዩባ አጋ ጤንጤኖ ተጀምሮ የነበረዉን ሪዕይ በማስቀጠል፣ ነባሩን የገዳ ስርዓት ባህላዊ እሴቶቹን ሳይለቅ እንዲጠናከር መስራት፤ የባህል ማዕከላትን ማደራጀት የመሳሰሉ ተግባራትን ማከናወን ሲሆን የታለመለትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ደግሞ ከቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የገዳ እና ባህል ጥናት እንስቲትዩት ጋር በአጋርነትና በትብብር በገዳ ስርዓት ዙሪያ አብሮ ለመስራት ይህ የመግባቢያ ሠነድ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ተፈርሟል።

Pages