በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ “ባህላዊ ህክምና እና ሀገር በቀል የህክምና ልምዶች ከዘመናዊ ጤና አጠባበቅ ሥርዓት አንፃር፡ ከማወቅ እስከ ትብብር” በሚል መሪ ቃል ዎርክሾፕ ተካሄደ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ ህዳር 01/2018 ዓ.ም (ቡሆዩ)

በሀገር በቀል ህክምና ዕዉቀት ዙሪያ በተናጠል የሚሠሩ ሥራዎችን የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በአንድ ላይ በማገናኘት በዘርፉ የተሻለ ሥራ ለመሥራትና የተመራማሪዎችን አቅም ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ ዎርክሾፕ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከጤና ሚኒስቴር፤ከተለያዩ ወረዳዎች የተጋበዙ የባህልና ቱሪዝም የሥራ ኃላፊዎች እና ከተለያዩ አካባቢዎች የተጋበዙ የባህል ህክምና አዋቂዎች በተገኙበት ዎርክሾፕ ተካሂዷል፡፡

የቡሌ ሆራ የኒቨርሲቲና የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ፡፡

አዲስ አበባ፣ ህዳር 04/2018 ዓ.ም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ

በቡሌ ሆራ የኒቨርሲቲ አካዳሚክ፤ምርምር፤ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬ የተመራ ልዑክ በዛሬዉ ዕለት አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንሲቲትዩት ቢሮ በመገኘት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲቲና የኢትዮጵያ ደን እና ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 07/2018 ዓ.ም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ

ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው ያለውን ብዝሃ ሕይወት በአግባቡ በመጠበቅ ከቱርዝም የሚገኘው ገቢ የሀገር ኢኮኖሚን መደገፍ እንዲችል ከደን እና ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ከባልሥጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኩመራ ዋቅጀራ ጋር የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ፣ምርምር፣ቴክኖሎጅ ሽግግርና ማህብረሰብ አግልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬ ተፈራርሟል።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከፋነ - አጋ ፋዉንዴሽን ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡

ህዳር 20/2018 ዓ.ም፡ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

ይህ ምሥረታ ወይም ፋዉንዴሽኑ ህዳር 23/2016 ዓ/ም በይፋ ስራ የጀመረ ሲሆን ፤ የተቋቋመበት ዋና ዓላማ ቀደም ሲል 72ኛ የጉጂ አባ ጋዳ በነበሩና የክብር ዶኮቶሬት ተሸላሚ በዩባ አጋ ጤንጤኖ ተጀምሮ የነበረዉን ሪዕይ በማስቀጠል፣ ነባሩን የገዳ ስርዓት ባህላዊ እሴቶቹን ሳይለቅ እንዲጠናከር መስራት፤ የባህል ማዕከላትን ማደራጀት የመሳሰሉ ተግባራትን ማከናወን ሲሆን የታለመለትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ደግሞ ከቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የገዳ እና ባህል ጥናት እንስቲትዩት ጋር በአጋርነትና በትብብር በገዳ ስርዓት ዙሪያ አብሮ ለመስራት ይህ የመግባቢያ ሠነድ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ተፈርሟል።

Pages