የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሙያዎች ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላት የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሰጡ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 24፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በሥልጠናው ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና በየደረጃው ያሉ የካውንስል አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ በሥልጠናው ቦታ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ሥልጠናው በመንግስት ደረጃ ከተሰጠን ተልዕኮና ዓላማ አንፃር በምን ደረጃ ላይ እንዳለን ራሳችንን የምንፈትሽበትና የታዩብን ውስንነቶች ካሉም በቀጣይ አሻሽለን በተሟላ ሁኔታ መፈፀም እንዲንችል አቅጣጫ የሚያሳየን ሥልጠና ነው በማለት የገለፁ ሲሆን ይህንኑ በሚመለከት ሥልጠናውን ለመስጠት በዩኒቨርሲቲው የተገኙትን የትምህርት ሚኒስቴር ባለሙያዎችን አመስግኗል።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ አስተባባሪነት ``AI for Academic Research`` በሚል ርዕስ ዎርክ ሾፕ ተካሄደ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 22፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በዎርክ ሾፑ ላይ ኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ከሁሉም ትምህርት ክፍሎች የተመለመሉ መምህራን የተሳተፉ ሲሆን ከተመራቂ የመጀመሪያ ዲግሪና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች መካከልም የተወጣጡ ተማሪዎች ስለ መሳተፋቸው ተገልፆዋል።
ዎርክሾፑን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት የኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ዲን መ/ር አሰፋ ሰንበቶ በአሁኑ ሰዓት እየኖርን ያለነው በዲጂታል ዓለም ውስጥ መሆኑንና ይህም ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ ለውጥ እያሳዬ መምጣቱን የጠቀሱ ሲሆን በሀገራት ኢኮኖሚ ዕድገት ዙሪያም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ስለመሆኑ አስረድቷል።

ጤና ኢንስቲትዩት ዕጩ ዶ/ር ዳዊት ገልገሎ እና ዕጩ ዶ/ር ሽፈራው ገልቹ የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት (phd) የመመረቂያ የምርምር ጽሑፋቸውን አቀረቡ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 22፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
ዕጩ የሦስተኛ ዲግሪ(Phd) ተመራቂዎቹ የምርምር ሥራቸውን አዲቫይዜሮቻቸውን ጨምሮ የውጪ ገምጋሚዎችና ሌሎች ተጋባዥ ምሁራን በተገኙበት በማቅረብ በተሳካ ሁኔታ ጨርሰዋል።
በዕለቱም ዩኒቨርሲቲው በም/ፕሬዝዳንት ማዕረግ የጤና ኢንስቲትዩት ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሳፋይ ኤለማ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን ዕጩ የሶስተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች ኢንስቲትዩቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያስመርቃቸው በመሆኑ ለኢንስቲትዩቱም ልዩ ቀን መሆኑን የገለፁ ሲሆን ተመራቂዎቹም በወጣትነት ዕድሜያቸውና በአጭር ጊዜ ለዚህ ስኬት የበቁበት መንገድ ለሌሎች አስተማሪና የይቻላል መንፈስን ያስተማረ ነዉ ሲሉ ገልፀዋል።

Biodiversity Conversation and Ecotourism; and Wildlife Managment and Ecotoursim`` በሚል ትምህርት ፕሮግራም ዙሪያ National Level Curriculum Review ተካሄደ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 21፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት`` Biodiversity Conversation and Ecotourism; and Wildlife Managment and Ecotoursim`` በሚል ትምህርት ፕሮግራም ዙሪያ National Level Curriculum Review ተካሄደ።
በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ደረጃ የሚሰጡ ተቀራራቢ ይዘት ያላቸው የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞችን በመገምገም በስያሜ ማስተካከያ እና በተዋሄዱ ፕሮግራሞች ዙሪያ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ የማድረግ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ።

Pages