በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ አስተባባሪነት ``AI for Academic Research`` በሚል ርዕስ ዎርክ ሾፕ ተካሄደ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 22፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በዎርክ ሾፑ ላይ ኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ከሁሉም ትምህርት ክፍሎች የተመለመሉ መምህራን የተሳተፉ ሲሆን ከተመራቂ የመጀመሪያ ዲግሪና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች መካከልም የተወጣጡ ተማሪዎች ስለ መሳተፋቸው ተገልፆዋል።
ዎርክሾፑን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት የኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ዲን መ/ር አሰፋ ሰንበቶ በአሁኑ ሰዓት እየኖርን ያለነው በዲጂታል ዓለም ውስጥ መሆኑንና ይህም ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ ለውጥ እያሳዬ መምጣቱን የጠቀሱ ሲሆን በሀገራት ኢኮኖሚ ዕድገት ዙሪያም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ስለመሆኑ አስረድቷል።

ጤና ኢንስቲትዩት ዕጩ ዶ/ር ዳዊት ገልገሎ እና ዕጩ ዶ/ር ሽፈራው ገልቹ የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት (phd) የመመረቂያ የምርምር ጽሑፋቸውን አቀረቡ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 22፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
ዕጩ የሦስተኛ ዲግሪ(Phd) ተመራቂዎቹ የምርምር ሥራቸውን አዲቫይዜሮቻቸውን ጨምሮ የውጪ ገምጋሚዎችና ሌሎች ተጋባዥ ምሁራን በተገኙበት በማቅረብ በተሳካ ሁኔታ ጨርሰዋል።
በዕለቱም ዩኒቨርሲቲው በም/ፕሬዝዳንት ማዕረግ የጤና ኢንስቲትዩት ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሳፋይ ኤለማ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን ዕጩ የሶስተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች ኢንስቲትዩቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያስመርቃቸው በመሆኑ ለኢንስቲትዩቱም ልዩ ቀን መሆኑን የገለፁ ሲሆን ተመራቂዎቹም በወጣትነት ዕድሜያቸውና በአጭር ጊዜ ለዚህ ስኬት የበቁበት መንገድ ለሌሎች አስተማሪና የይቻላል መንፈስን ያስተማረ ነዉ ሲሉ ገልፀዋል።

Biodiversity Conversation and Ecotourism; and Wildlife Managment and Ecotoursim`` በሚል ትምህርት ፕሮግራም ዙሪያ National Level Curriculum Review ተካሄደ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 21፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት`` Biodiversity Conversation and Ecotourism; and Wildlife Managment and Ecotoursim`` በሚል ትምህርት ፕሮግራም ዙሪያ National Level Curriculum Review ተካሄደ።
በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ደረጃ የሚሰጡ ተቀራራቢ ይዘት ያላቸው የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞችን በመገምገም በስያሜ ማስተካከያ እና በተዋሄዱ ፕሮግራሞች ዙሪያ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ የማድረግ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ።

Bule Hora University signed MoU with Refocus Africa Investors Network Limited.

May 16/2025: Bule Hora University
Bule Hora University (Ethiopia) and Refocus Africa Investors Network Limited (Tanzania) today announced a strategic collaboration to advance education, innovation, and sustainability across Africa. The partnership was formalized through the signing of a Memorandum of Understanding (MoU) at a ceremony held at the Inter Luxury Hotel in Addis Ababa, Ethiopia.

Pages