በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የምርምር ሥራዎች ዙሪያ የዉስጥ ግምገማ ተካሄደ፡፡
Posted by admin on Thursday, 9 October 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም፣ 2018 (ቡሆዩ)
በዩኒቨርሲቲዉ የምርምር፤ስርፀትና ሥነ ምግባር ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት ከተለያዩ ኮሌጆች የተወጣጡ ምሁራን የምርምር ሥራዎቻቸዉን አቅርበዉ የዉስጥ ግምገማ ተካሂዶባቸዋል፡፡
በዕለቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ምርምር፤ስርፀትና ሥነ ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር አብነት በቀለ ሲሆኑ ለዉስጥ ግምገማ የቀረቡ የምርምር ሥራዎች በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ዳይሬክቶሬቱ ጭብጥ ተኮር የምርምር ሥራዎችን ለማሰራት ያስቀመጠዉን አቅጣጫ ተከትሎ በተለያዩ ኮሌጆች ምሁራን ፕሮፖዛል ቀርበዉ፤ተገምግመዉና ተቀባይነት አገኝተዉ የተሠሩ የምርምር ሥራዎች ስለመሆናቸዉ በመግለጽ በጋራ የዉስጥ ግምገማ መደረጉ የእርስ በርስ ልምድ ልዉዉጥ እንዲደረግ ታሳቢ በማድረግ እንደ ሆነ ገልፀዋል፡፡
Bule Hora University delegates are currently in Zagreb, Croatia, participating in the EU-funded DigHealth project workshop.
Posted by admin on Thursday, 9 October 2025Bule Hora University, October 8, 2025 (BHU)
This pivotal workshop is a continuation of sessions previously held in Greece and is meticulously designed to build advanced capabilities. The core focus areas include:
1. Advanced Telemedicine Monitoring
2. Refining Teleconsultation Skills
3. Practical Hospital Applications
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ማህበር ጠቅላላ ጉባዔ ተካሄደ፡፡
Posted by admin on Thursday, 9 October 2025መስከረም 22/2018 ዓ.ም :ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
በዩኒቨርሲቲዉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ መልክ የተመረጡት የመምህራን ማህበር ሥራ አስፈፃሚዎች ከተመረጡበት ጊዜ ወዲህ የተከናወኑትን ተግባራትና ሌሎችንም ጉዳዮች ጨምሮ የጉባዔዉ ተሣታፊ መምህራን በተገኙበት አቅርቦ ሰፊ ዉይይት ተካሂዷል፡፡
በማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ፤ምርም፤ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬና የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አካሉ አሰፋ ተገኝቷል፡፡
























































