የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የኤሌክትሮኒክስ ባንኪንግ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ሰጠ፡፡

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የኤሌክትሮኒክስ ባንኪንግ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ሰጠ፡፡
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡሌ ሆራ ቅርንጣፍ ጋር በመተባበር ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፋይናንስ አስተዳደር ባለሙያዎች በኤሌክትሮኒክስ ባንኪንግ ጋር በተያያዘ ስልጠና ሰጠ፡፡
በስልጠናዉ ላይ ዶ/ር ታምሩ አኖሌ (የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ) ፣ዶ/ር ሮባ ደንቢ (የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ) እና ዶ/ር ጉሚ ቦሩ (የምርምርና የማህበረሰብ  አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት) ተገኝተዋል፡፡
የኤፌዲሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ባወጣው አዋጅ መሰረት የፌዴራል ፋይናንስ ተቋማት ማንኛውንም ክፍያ በዲጅታል ኤሌክትሮኒክሲ የክፍያዎች መረብ መፈፀም እንዳለበት ይደነግጋል:: 

International Virtual Conference On Transforming Agricultural Advisory Services to Mitigate the Effects of the Pandemic for Farmers Welfare.

Vellore Institute of Technology in collaboration with Bule Hora University and other 2 Universities are organizing an International conference on  “Transforming Agricultural Advisory Services to Mitigate the Effects of the Pandemic for Farmers Welfare”.

የመፅሀፍ ድጋፍ ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

የመፅሀፍ ድጋፍ ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
የኢትዮጲያ እውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማህበር ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመፅሀፍ ድጋፍ አደረገ።
በድጋፉ የተበረከቱት መፅሀፍት ብዛት 231/ሁለት መቶ ሰላሣ አንድ/ ሲሆኑ፤ለህክምና ትምህርት የሚጠቅሙ ናቸውም ተብሏል። የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሰቲ የጤና ኢንስቲቲዩት ዲን መ/ር ታከለ ኡቱራ የተበረከቱት መፅሀፍት በኢንስቲቲዩት የሚስተዋሉትን የመፅሀፍት እጥረት ለመቅረፍ አጋዥነታቸው ከፍተኛ ነው ብለዋል። መ/ር ታከለ ኡቱራ በሂደት ላይ ያለ የመፅሀፍ ግዥ እንዳለ አስታውሰዋል። እንደ ሜዲስንና አነስቴዥያን ያሉ ትምህርቶች የመፅሀፍት እጥረት እንደሚስተዋልባቸው ገልፀዋል።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ "አልረሳውም እኔም የኢትዮጵያ ወታደር ነኝ "

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ "አልረሳውም እኔም የኢትዮጵያ ወታደር ነኝ!" በሚል መሪ ቃል በሰሜን እዝ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የተፈፀመ የግፍ ተግባር ታስቦ ዋለ።
የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሀገርን ዳርድንበር ከማስከበር ባሻገር ለአለም አቀፍ፣ ለአህጉራዊና ቀጠናዊ ሠላም መረጋጋትም የደም እና የህይወት ዋጋ በመክፈል ለሠላም ዘብ የቆመ የሀገር ደጀን ነዉ።
የሀገርን ድንበር እና ሉዓላዊነት ለማስከበር ከ20 ዓመታት በላይ የሀገርን ዳር ድንበር ሌት ተቀን ሲያስከብር በቆየው የሰሜኑ ዕዝ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ዘግናኝ እና ኢ-ሰብዓዊ የሆነ ጥቃት ተፈጽሟል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲም ይህንን ቀን በማሰብና የሕይወት መስዋዕትነት ለከፈለውና እየከፈለ ለሚገኘው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ደጀንነቱን ለማረጋገጥ ጥቅምት 24/2014 ዓ.ም ከማለዳው 2:30 ጀምሮ በዩኒቨርስቲው ኦዳ አዳራሽ ፊት ለፊት መርሃግብሩን አካሂዷል።

Pages